Skip to Content

በእንስሳት ህክምና የክሊኒካል ላብራቶሪ ክህሎት ስልጠና እየተሰጠ ነው

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ የእንስሳት ህክምና ፋካልቲ ከብሩክ ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ከ3ኛ እስከ 5ኛ ዓመት ለሚገኙ ተማሪዎች በእንስሳት ህክምና የላብራቶሪ ሞዴል አዘገጃጀት ክህሎትን ለማሳደግ እንዲሁም የጋማ እንስሳት ጤናን ለማስጠበቅ የሚያስችል እውቀት ላይ ያተኮረ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል።

የኮሌጁ ዲን ዶ/ር ዙፋን በደዊ እንደተናገሩት "ብሩክ ኢትዮጵያ" በእንስሳት ህክምናና ደህንነት ዙሪያ በርካታ ሀገር አቀፍ ተጽዕኖ መፍጠር የቻሉ ስራዎችን እየሰራ ያለ ግብረሰናይ ድርጅት መሆኑን አስታውሰው በተለይም በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የእንስሳት ህክምና አሰጣጥ ላይ ተጨባጭ ለውጥ ያመጡ ስልጠናዎችን፣ የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ እንዲሁም የላብራቶሪ ግንባታ ስራዎችን ማከናወኑን ገልጸዋል።


የእንስሳት ህክምና ፋካሊቲ ዲን ዶ/ር አመነ ፈቃዱ በበኩላቸው ቀደም ሲል ለክፍሉ መምህራን የተሰጠው ተመሳሳይ ስልጠና የተሻለ ውጤት ማስገኘቱን ከግንዛቤ በማስገባት ይኸው ስልጠና ወደ ተማሪዎች መውረድ እንዳለበት ከ"ብሩክ ኢትዮጵያ" ጋር መግባባት መፈጠሩን ጠቁመው በዚህ መሰረት ከ3ኛ-5ኛ አመት ድረስ ያሉ የእንስሳት ህክምና ተማሪዎች የህክምና ሂደቱን ውጤታማና የእንስሳቱን ደህንነት በማይጎዳ መልኩ ተግባራዊ ማድረግ የሚችሉበትን የእውቀትና ክህሎት ማሳደጊያ ስልጠና እንዲያገኙ ተደርጓል ብለዋል።


ስልጠናው ባለፈው ሳምንት ለ5ኛ አመት ተማሪዎች መሰጠት መጀመሩን የገለጹት በብሩክ ኢትዮጵያ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የእንስሳት ጤና ኦፊሰር ዶ/ር ትንሳኤ ከበደ በተለይም የጋማ እንስሳት ጤናና ደህንነት ለማስጠበቅ በክሊኒካል ላብራቶሪ ክህሎት ላይ ትኩረቱን አድርጎ እንደሚሰጥ ጠቁመዋል።

Share this post
Tags
Archive
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ራስ ገዝ የማድረግ ሂደት የሁሉንም ባለድርሻዎች ድጋፍና ትብብር እንደሚጠይቅ ተጠቆመ