Skip to Content

ምክትል ፕሬዝዳንቶችና የኮሌጅ አመራሮች የአፈፃፀም ውል ኮንትራት ተፈራረሙ

ምክትል ፕሬዝዳንቶችና የኮሌጅ አመራሮች የአፈፃፀም ውል ኮንትራት ተፈራረሙ::


የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንቶችና የፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ኃላፊ ከኮሌጅ ዲኖች: የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር: የህ/ጤ/ሣ/ኮ ቺፍ ኤግዘኪዩቲቭ ዳይሬክተር እና ከዳዬ ካምፓስ ኤግዘኪዩቲቭ ዳይሬክተር ጋር ቁልፍ የአፈፃፀም አመላካቾችን የያዘውን የአፈፃፀም ውል ኮንትራት ዛሬ በአፍሪካ ህብረት አዳራሽ የዩኒቨርሲቲው ካውንስል አባላት በተገኙበት ተፈራርመዋል::


የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ችሮታው አየለ ስለ ውሉ አስፈላጊነት ባስረዱበት ንግግራቸው ሁሉም የሥራ ክፍሎች የየድርሻቸውን ኃላፊነት ቆጥረው ተረክበው ውጤቱንም እንዲያመጡ የወረደና ተጠያቂነትን የሚያስከትል መሆኑን ገልፀዋል::


በዚህም መሰረት ዛሬ ከከፍተኛ አመራሮች ጋር ውል የገቡት የየኮሌጁ አመራሮች በሚቀጥለው ሳምንት ደግሞ በተዋረድ ከየትምህርት ክፍል ኃላፊዎች ጋር ውል ገብተው አፈፃፀሙን የመምራት ግዴታ እንደተጣለባቸው እንዲረዱ መመሪያ የሰጡት ፕሬዝዳንቱ ከፍተኛ አመራሩም ሁሉንም የሥራ ሂደቶች የመከታተልና አስፈላጊውን ሁሉ አስተዳደራዊ ድጋፍ የማድረግ ግዴታ እንዳለባቸው ተናግረዋል::



Share this post
Tags
Archive
HU has graduated 1000 students