Skip to Content

በንብ ማነብ ሥራ ላይ ለተሰማሩ ወጣቶች ድጋፍ ተደረገ

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ከኖርዌይ መንግስት ጋር ባለው የረጅም ግዜ ትብብር በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ በሲዳማ ክልል ዳሌ ወረዳ በናራሞ ዴላ 01 ቀበሌ ተደራጅተው በንብ ማነብ ስራ ላይ ለተሰማሩ ሥራ አጥ ወጣቶች ማህበር 20 ዘመናዊ የንብ ቀፎዎች: የንብ መንጋ: የሥራ ማስጀመሪያ የንብ መኖና ለዘመናዊ የማር ምርት ማዘጋጃ የሚያስፈልጉ በአጠቃላይ ከአንድ ሚሊዮን ብርበላይ የሚያወጡ ሙሉ ግብዓቶችን አበርክቷል።


የዩኒቨርሲቲው የትብብር ፕሮጀክቶች ማስ/ዳይሬክተር ፕ/ር መብራቱ ሙላቱ በርክክቡ ላይ እንደገለፁት የማህበረሰብ አገልግሎት ስራዎች ውጤታማነት የሚለካው በሚፈጥሩት የስራ ዕድል ብዛት፣ በሚፈቱትና በሚያቃልሉት የማህበረሰቡ ችግሮች፣ በዘላቂነታቸውና ፍትሐዊነታቸው በመሆኑ ለወጣቶቹ የተደረገው ሥራ ማስጀመሪያ ድጋፍ በሙያዊ ስልጠናና ተጨማሪ ድጋፍና ክትትል ዘላቂ ውጤት እንዲመዘገብ እንሰራለን ብለዋል።



የሀ/ዩ/ማህበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ ማርቆስ ፍሰሐ ዩኒቨርሲቲው በዋነኛነት በሲዳማ ክልል የሚገኙ ወጣቶችን የስራ እድል ተጠቃሚዎች በማድረግ ራሳቸውንና ማህበረሰባቸውን መጥቀም እንዲችሉ በተለያዩ ዘርፎች ሰብል ከመንግስትና መንግታዊ ካልሆኑ ተቋማት ጋር በትብብር እየሰራ ይገኛል ብለዋል።


የዳሌ ወረዳ እንስሳት ሀ/ል/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሻላሞ ሹራሞ በበኩላቸው የዩኒቨርሲቲው ድጋፍ አርሶአደርና አርብቶአደሮችን እንዲሁም የእንሰሳት ጤና ባለሙያዎችን ከማሰልጠን ባለፈ ወደ ሥራ ፈጠራ እንዲገቡ የቁሳቁስ ድጋፍ በማድረግ ማህበራዊ ኃላፊነቱን በሚገባ እየተወጣ እንደሚገኝ በመግለጽ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።


Share this post
Tags
Archive
ለዳዬ ካምፓስ ተመራቂ ተማሪዎች የስራ ፈጠራ ክህሎትና የመቀጠር ዝግጁነት ስልጠና ተሰጠ።