Skip to Content

የበንሳ ዳዬ ካምፓስ  አመታዊ የምርምር አውደ ጥናት አካሄደ

የበንሳ ዳዬ ካምፓስ  አመታዊ የምርምር አውደ ጥናት አካሄደ


በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የበንሳ ዳዬ ካምፓስ በ2016 ዓ.ም ተጀምረው የተጠናቀቁ አምስት የዲሲፕሊነሪ ምርምሮች የገመገመበት ዓመታዊ መድረክ አካሂዷል::


የሀ/ዩ የምርምር ፕሮግራም አስተባባሪ ዶ/ር ንጉሴ አፈሻ በመክፈቻ ንግግራቸው እንደገለጹት ሀዋሳ እንደ ምርምር ዩኒቨርሲቲነቱ ወቅታዊና ችግር ፈቺ ምርምሮችን የማካሄድ ኃላፊነት ስላለበት ሁሉም ኮሌጆች በየወቅቱ የሚሰሯቸውን ምርምሮችን በቁጥርና በጥራት ማላቅ ይጠበቅባቸዋል ብለዋል። ዶ/ር ንጉሴ መንግስት የምርምር ዩኒቨርሲቲዎችን ለመደገፍ ለምርምር የሚመደበውን በጀት ከዓመታዊው በጀታቸው ከ2% ወደ 5% እንዲያድግ ማድረጉን ተከትሎ ከመጪው አመት ጀምሮ ጭብጥ ተኮር ምርምሮች የበለጠ ትኩረት እንደሚሰጣቸውም አክለዋል።



የዳዬ ካምፓስ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር ፍሬው ካሳ በበኩላቸው ካምፓሱ በቁጥር ዝቅተኛ የምርምር ስራዎችን ከሚያከናውኑ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጆች አንዱ እንደነበረ አስታውሰው በም/ት/ም/ፕሬዚደንት ጽ/ቤት በኩል በተደረገለት ከፍተኛ ድጋፍ አመርቂ ውጤት መመዝገቡን ገልጸዋል። የተሰሩ ምርምሮችን በጥልቀት በባለሙያዎች መገምገም የተገኘባቸውን ክፍተቶች በመለየት የተሻለ ሥራ ለመስራትና ወደ ተግባር ለማስገባት ስለሚያግዝ አውደጥናቶቹ ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ዶ/"ር ፍሬው ገልጸዋል።


የበንሳ ዳዬ ካምፓስ ምርምርና ትብብር ተ/ዲን አቶ ማቴዎስ በዕለቱ ከካምፓሱ ተመራማሪዎች የተሰሩት አምስት የምርምር ጽሁፎች ቀርበው ሳይንሳዊ መንገድ ተከትለው ስለመሰራታቸው: ምን ያህል በተግባር ችግር ፈቺ ሊሆኑ እንደሚችሉ ከተሳታፊዎች ጥያቄዎችና አስተያየቶች በመቅረባቸው ለሌሎች ተመራማሪዎችም ልምድ የሚቀስሙበት መድረክ መሆኑን ተናግረዋል።


Share this post
Tags
Archive
SLL360 Project Organizes Annual Visit and Leadership Meeting