Skip to Content

ለድህረምረቃ ተማሪዎች የስታቲስቲክስ ሶፍትዌሮች አጠቃቀም ስልጠና ተሰጠ።

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ የስታቲስቲክስ ት/ክፍል ለዩኒቨርሲቲው የድህረ ምረቃ ተማሪዎች በምርምር ስራዎች ላይ አጋዥ የሆኑትን የ"SPSS-R" እና "STATA" ሶፍትዌሮች አጠቃቀም ላይ የሁለት ቀናት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ከየካቲት 27-28/2017 ዓም እየሰጠ ነው።


ሶፍትዌሮች በምርምር ስራ ላይ ከመረጃ አሰባሰብ እስከ የመጨረሻው ውጤት ትንታኔ ድረስ ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወቱ የገለጹት የተ/ቀ/ሳ ኮሌጅ ዲን ዶ/ር ዙፋን በደዊ ተመራማሪዎች እነዚህን ሶፍትዌሮች ጠንቅቀው ማወቅና መጠቀም እንዲችሉ ተደጋጋሚ ስልጠናዎች ያስፈልጋሉ ብለዋል። ዶ/ር ዙፋን የስታቲስቲክስ ትምህርት ክፍል መምህራን በራሳቸው ተነሳሽነት በየዓመቱ ተመሳሳይ ስልጠና በመስጠት አዎንታዊ ድርሻ እየተወጡ እንደሆነ ገልፀው ምስጋናቸውን በኮሌጁ ስም አቅርበዋል።



የስታቲስቲክስ ት/ክፍል ኃላፊ መምህርት ውብእጅግ እንየው በበኩላቸው ስልጠናው በዩኒቨርሲቲው ስር ለሚገኙ የሁሉም ኮሌጆች የማስተርስና ዶክትሬት መርሃግብር ተማሪዎች የተዘጋጀና በት/ክፍሉ አንጋፋ መምህራን እየተሰጠ እንደሆነ ገልፀው ሶፍትዌሮቹ መረጃን በማጥራት፣ ኮድ በማድረግ፣ በመተንተን እንዲሁም ውጤት በማስቀመጥ የምርምር ስራዎችን የምያቀሉ በመሆናቸው ሰልጣኝ ተመራማሪዎች ትኩረት ሰጥተው ስልጠናውን በመከታተል ተጠቃሚነታቸውን እንደሚያረጋግጡ እምነት አለኝ ብለዋል።


Share this post
Tags
Archive
ለኮሌጁ መምህራን በግራንት ፕሮፖዛል አጻጻፍ ላይ ስልጠና ተሰጠ።